አቶ ተስፋዬ ሰሙንጉስ እባላለሁ። በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከ April 17, 2015 ጀምሮ
ላለፉት 7 አመተታ በተለያዩ ዘርፎች ማህበረሰባችንን በቅንነት በነፃ እያገለገልኩኝ እገኛለሁ።
በተለይ ደግሞ “ማወቅ መልካም ነው ያወቁትን ማሳወቅ ፍፁም በጎነት ነው ”
በሚል መሪ ቃል በርካታ የቴክኖሎጂ ትምህርቶችን ለማህበረሰቤ
ዘር ፤ ብሔር ፤ ሀይማኖት ሳይገድበኝ የማውቀውን አሳውቄአለሁኝ።
አሁንም ባለኝ ትርፍ ጊዜ የማውቀውን በማሳወቅ ላይ እገኛለሁ።
በፈረንጆች ከ 2018 ወዲህ ደግሞ ማወቅ መልካም ነው የሚለውን አቋሜን
በሀይማኖት ፤ በፖለቲካ ፤ በቴክኖሎጂ ፤ በብዙ ማህበራዊ ተሳትፎ በሚያስፈልጋቸው
ተሳትፎዎች ላይ ሁሉ በመሳተፍ በፅሁፍ ፤ በቪዲዮ ፤ በተለያዩ ዘመኑ ባፈራቸው
የማህበራዊ ሚዲያዎችን መንገዶች በመጠቀም ሀሳቤን በነፃነት በተለይ ለትውልድ ሀገሬ
ይጠቅማል የምለውን ሁሉ ማንነትን ፤ ብሔርን ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ሳልደግፍ በግል የተሰማኝን
መልካም ነገር ብቻ በማቅረብ ህብረተሰቤን በማገልገል ላይ የምገኝ በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት ደግሞ ካናዳዊ የሆንኩኝ ግለሰብ ነኝ።